Logo

    የጥቁሮች የዘር ጭቆናን ለማስቆም ብቸኛው መፍትሄ በኢኮኖሚ እራስን መቻል - ዶክተር ፍሰሃ እሸቱ - ጁላይ 15, 2021

    amJuly 15, 2021
    What was the main topic of the podcast episode?
    Summarise the key points discussed in the episode?
    Were there any notable quotes or insights from the speakers?
    Which popular books were mentioned in this episode?
    Were there any points particularly controversial or thought-provoking discussed in the episode?
    Were any current events or trending topics addressed in the episode?

    Recent Episodes from ጋቢና ቪኦኤ - የአሜሪካ ድምፅ

    የተሰናባቹ 2013 ዓ.ም ፈታኝ ሁነቶች እና የአዲሱ አመት ተስፋ - ሴፕቴምበር 10, 2021

    የተሰናባቹ 2013 ዓ.ም ፈታኝ ሁነቶች እና የአዲሱ አመት ተስፋ - ሴፕቴምበር 10, 2021
    ኢትዮጵያውያን እየተሰናበቱት ያለው 2013 ዓ.ም በብዙ ፈታኝ ሁነቶች የተሞላ ነበር። አመቱ ላለፉት አስር ወራት በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ጨምሮ፣ በርካታ ግጭቶች፣ ኮቪድ 19 ወረርሽኝ፣ የዋጋ ግሽበትና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች የተስተናገዱበት ሆኖ አልፏል ። እነዚህን ተግዳሮቶች ምን ይመስሉ ነበር? በመጪው 2014 ዓመተ ምህረትስ ምን ይጠበቃል?

    ለተቸገሩ ህሙማን እና አስታማሚዎች ማረፊያ የሆነችው ሀኪም - ሴፕቴምበር 03, 2021

    ለተቸገሩ ህሙማን እና አስታማሚዎች ማረፊያ የሆነችው ሀኪም - ሴፕቴምበር 03, 2021
    አሜሪካ በየአመቱ ለአፍሪካ ወጣት መሪዎች በምታዘጋጀው የማንዴላ ፌሎውሺፕ በዚህ አመት ከኢትዮጵያ ከተመረጡት መሀከል ጎጆ የህሙማን መጠለያ ተቋምን የመሰረተችው ዶክተር ሰላሜነሽ ፅጌ አንዷ ናት። ተቋሙ ከኢትዮጵያ የገጠር ከተሞች ለተጨማሪ ህክምና አዲስ አበባ የሚመጡ፣ ማረፊያ በማጣትና ገንዘባቸውን ለህክምና በመጨረስ ለጎዳና ህይወት የሚዳረጉ ህሙማንን በጊዜያዊነት የሚያስጠልል ሲሆን ባለፉት ሶስት አመታት ውስጥ ከ81 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህሙማን ረድቷል።

    ልጆችዎ ትምህርት ቤት መሄድ ቢጠሉ ምን ያደርጋሉ? - ሴፕቴምበር 03, 2021

    ልጆችዎ ትምህርት ቤት መሄድ ቢጠሉ ምን ያደርጋሉ? - ሴፕቴምበር 03, 2021
    ህፃናት የትምህርት መማሪያ ጊዜያቸው ደርሶ ወደ ትምህርት ቤት ሲገቡ ወይም ካደጉ በኃላ በህይወታቸው በሚደርሱ የተለያዩ ገጠመኞች ምክንያት ትምህርት ቤት መሄድን ሊፈሩና ሊጠሉ ይችላሉ። በተለይ ከፍ እያሉ ሲሄዱ ትምህርት ቤት ውስጥ ሊያጋጥማቸው የሚችል ዝቅተኛ የመሆን ስሜት፣ የአካባቢ መቀየር፣ በወላጅ መሀል የሚደርስ ፍቺ ወይም ሞት ልጆች ትምህርት ቤት መሄድን እንዲጠሉ ሊያደርጋቸው ይችላል። ይህ ሁኔታ ሲያጋጥም ልጆች ፍርሀታቸውን ማሸነፍ እንዲችሉ ምን ማድረግ ይቻላል?

    'ዓለምን በቀጣይ ከሚያሰጓት ወረሽኞች ለመከላከል የሚያጠናው ግሎባል ዋን ሄልዝ' ቆይታ ከፕሮፌሰር ወንድወሰን አበበ ጋር - ኦገስት 26, 2021

    'ዓለምን በቀጣይ ከሚያሰጓት ወረሽኞች ለመከላከል የሚያጠናው ግሎባል ዋን ሄልዝ' ቆይታ ከፕሮፌሰር ወንድወሰን አበበ ጋር - ኦገስት 26, 2021
    ግሎባል ዋን ሄልዝ ኢንሺየቲቭ ወይም አንድ የዓለም ጤና ተነሳሽነት በአሜሪካ ሃገር በሚገኘው በኦሃዮ ዩኒቨርሲቲ አማካኝነት የተመሰረተ ሲሆን ዓላማውም ከአካባቢ፣ ከእንሣት እና ከሰዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው እንደ ኮቪድ 19፣ ኢቦላ፣ የእብድ ውሻ በሽታ፣ በነፍሳት ፣ በውሃ፣ በዓየር..የሚመጡ በሽታዎችን በኢትዮጵያ፣ ኬኒያ፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሜክሲኮ፣ ብራዚል እና ታይላንድ...እየተንቀሳቀሰ የሚያጠና ነው፡፡ ይሄ ተነሳሽነት ከተመሰረተ ዘንድሮ 10ኛ ዓመቱ ይዟል፡፡

    ከ500 በላይ ታዳጊዎችን ያሳተፈው የሕዋ ሳይንስ የክረምት ትምህርት ምን ምን ነገሮችን ይዟል? - ኦገስት 26, 2021

    ከ500 በላይ ታዳጊዎችን ያሳተፈው የሕዋ ሳይንስ የክረምት ትምህርት ምን ምን ነገሮችን ይዟል? - ኦገስት 26, 2021
    የኢትዮጵያ የሕዋ ሳይንስ ማኅበረሰብ ዘንድሮ ለየት ባለ ሁኔታ ልዩ መርሃግብር በመቅረጽ በአዲስ አበባ እና በአዳማ ከተማ በአጠቃላይ ቁጥራቸው 550  ለሚሆኑ የአንደኛ፤ የሁለተኛ ደረጃ እና የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ልዩ የክረምት ስልጠና አዘጋጅቶ ስለሕዋ ሳይንስ ሲያስተምር ቆይቷል፡፡ የመርሃግብሩ ተሳታፊ የሆኑ ሁለት ታዳጊዎች እና በኢትዮጵያ የሕዋ ሳይንስ ማኅበረሰብ ውስጥ መርሃግብሮች አስተባባሪ የሆኑትን አቶ ብሩክ ተረፈን ከጋቢና ቪኦኤ ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡

    የአይምሮ ጤና ከአካላዊ ጤና እኩል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል - ኦገስት 26, 2021

    የአይምሮ ጤና ከአካላዊ ጤና እኩል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል - ኦገስት 26, 2021
    የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ሀገራት የአይምሮ ጤና ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። በሽታው በቀጥታ በአይምሮጤና ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት በተጨማሪ ወረርሽኙ በሀገራት ኢኮኖሚ ላይ ባደረሰው ተፅእኖ ምክንያት ለአይምሮ ጤና ይደረግ የነበረው የገንዘብ ድጎማ በመመናመኑም ቀድሞውንም ደካማ የነበረው የህክምና አቅርቦት መቀነስ ችግሩን እያባባሰው ነው።

    የላም ወተት የተዘጋጀ የጸጉር ቅቤን አሽጋ ለዓለም የምትሸጠው ኢትዮጵያዊት - ኦገስት 10, 2021

    የላም ወተት የተዘጋጀ የጸጉር ቅቤን አሽጋ ለዓለም የምትሸጠው ኢትዮጵያዊት - ኦገስት 10, 2021
    ወ/ሮ ገነት ስለሺ የፎቶግራፍ ባለሞያ ስትሆን ነዋሪነቷ በአሜሪካ ሃገር ነው፡፡ በዓመታት ከሃገር ውጪ ቆይታዋ ያጋጠማት የጸጉር መርገፍ፣ መጎዳት እና ተስማሚ የሆነ ምርት ማጣት ችግር 'ሹሩባ የጸጉር ቅቤ' የተሰኘ ከላም ወተት የተመረተ የጸጉር ቅቤ ማምረቻ ተቋም እንድትከፍት እና ለዘመናት የቆየው የኢትዮጵያዊያን ጸጉርን ቅቤ የመቀባት ባህል ከኢትዮጵያ ውጪም እንዲስፋፋ ማድረግ እንድትችል አድርጓታል፡፡

    የቲያትር 100ኛ ዓመት በጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሲዘከር - ጁላይ 31, 2021

    የቲያትር 100ኛ ዓመት በጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሲዘከር - ጁላይ 31, 2021
    በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የቲያትር ጥበባት ክፍል ዘመናዊ ቲያትር በኢትዮጵያ የተጀምረበትን መቶኛ ዓመት በማሰብ ለሁለት ቀናት የቆየ መርሃግብር አካሂዷል፡፡ መርሃግብሩን የወልቂጤ፣ ደብረማርቆስ እና የወሎ ዩኒቨርስቲ የቲያትር ጥበብ ክፍሎችም የተሳተፉ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ የዘመናዊ ቲያትር ጅማሮን አስታኮ በመላው ሃገሪቱ የቲያትር ጥበብ እንዲነቃቃ እና እንዲያድግ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ስለቲያትር ቡድን አባላትም በቦታው ተገኝተው ውይይቱን ተካፍለዋል፡፡

    ሴትን ማስተማር ማህበረሰብን ማስተማር ነው - ጁላይ 29, 2021

    ሴትን ማስተማር ማህበረሰብን ማስተማር ነው - ጁላይ 29, 2021
    ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ትምህርት ቤት የሚገቡ ሴት ህፃናት ቁጥር ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ ቢሄድም አሁንም ሴት ተማሪዎች በሚያጋጥሟቸው በርካታ ተግዳሮቶች ምክንያት ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ይገደዳሉ። CAMFED (ትምህርት ለሴቶች ዘመቻ) የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ግን ላለፉት 18 አመታት ለተማሪዎችና ወላጆች የኢኮኖሚ አቅም በመፍጠር፣ እንዲሁም በአህጉሪቱ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን በማገዝ ከ4.8 ሚሊዮን በላይ ሴት ህፃናት በትምህርት ቤት እንዲቆዩ አድርጓል።