Logo

    ጤና - የአሜሪካ ድምፅ

    የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) ከአርባ በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ከዩናይትድ ስቴትስ በመላው ዓለም የሚያሠራጭ አገልግሎት ነው፡፡ ቪኦኤ በየሣምንቱ ወደ 1 ሺህ 500 ሰዓት ለሚሆን ጊዜ ዜና፣ መረጃዎችን፣ ትምህርታዊና ባሕላዊ ፕሮግራሞችን በዓለም ዙሪያ ወደ 123 ሚሊየን ለሚሆን ሰው ያደርሣል፡፡ የበለጠ ለማወቅ በ voanews.com ላይ ያግኙን፡፡
    am50 Episodes

    People also ask

    What is the main theme of the podcast?
    Who are some of the popular guests the podcast?
    Were there any controversial topics discussed in the podcast?
    Were any current trending topics addressed in the podcast?
    What popular books were mentioned in the podcast?

    Episodes (50)

    ራስን ማጥፋት የአይምሮ ጤና ቀውስ ውጤት ነው - ጃንዩወሪ 18, 2023

    ራስን ማጥፋት የአይምሮ ጤና ቀውስ ውጤት ነው  - ጃንዩወሪ 18, 2023
    ከቅርብ ግዜ ወዲህ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎች ራሳቸውን ስለማጥፋታቸው በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በተደጋጋሚ ይሰማል። ማህበራዊ ሚዲያው ከቀደመው ጊዜ የበለጠ መረጃዎችን እንድንሰማ ማድረጉ እንዳለ ሆኖ፣ ራስን ማጥፋትን በተመለከተ ጥናት ያጠናው የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በየእለቱ 30 ሰዎች ራሳቸውን እንደሚያጠፉና በዚህም ምክንያት ቢያንስ 150 ሰዎች ቀሪ ህይወታቸውን የሚወዱት ሰው ራሱን በማጥፋቱ በሚያስከትለው መዘዝ ጥላ ስር እንደሚያሳልፉ አመልክቷል።

    አፍሪካ ሲዲሲ በአፍሪካ አራተኛው ዙር የኮቪድ ግርሻ አሳስቦኛል አለ - ዲሴምበር 24, 2021

    አፍሪካ ሲዲሲ በአፍሪካ አራተኛው ዙር የኮቪድ ግርሻ አሳስቦኛል አለ - ዲሴምበር 24, 2021
    የአፍሪካ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠሪያ ተቋም አፍሪካ ሲዲሲ አመት በዓል እየደረሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት በአህጉሪቱ እየተመዘገበ ያለው አዲሱ የኮቪድ 19 ስርጭት አሳስቦኛል አለ፡፡ የማዕከሉ ዳይሬክተር ጆን ንኬንጋሶንግ የአፍሪካ ሃገራት ክትባትን ላይ አስገዳጅ ደንብ እንዲያወጡ እየገፋን እንገኛለን ብለዋል፡፡

    አዲሱ የኮቪድ ዝርያ እና የዩናይትድ ስቴትስ ጥብቅ መመሪያ - ዲሴምበር 04, 2021

    አዲሱ የኮቪድ ዝርያ እና የዩናይትድ ስቴትስ ጥብቅ መመሪያ - ዲሴምበር 04, 2021
    ዩናይትድ ስቴትስ አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ኦሚኮርን በሃገሪቱ መገኘቱ ካረጋገጠች ከ24 ሰዓት በኋላ ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን ወደ ሃገሪቱ የሚገቡ ዓለም አቀፍ ተጓዦችን በተመለከተ ጥብቅ መመሪያዎችን ያወጡ ሲሆን በሃመላው ሃገሪቱ በመጓጓዣዎች ላይ የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል መመሪያዎችም ለተራዘመ ጊዜ እንዲቆዩ አድርገዋል፡፡ ፕሬዘዳንቱ በተጨማሪም 200 ሚሊየን የኮቪድ 19 ክትባቶች በቀጣይ ወር ለሌሎች ሃገራት እንደሚለገሱም ቃል ገብተዋል፡፡

    የጽንስ ማቋረጥ እሰጥ አገባ በዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ፍ/ቤት - ዲሴምበር 02, 2021

    የጽንስ ማቋረጥ እሰጥ አገባ በዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ፍ/ቤት - ዲሴምበር 02, 2021
    በትላንትናው ዕለት የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ፍ/ቤት ጽንስ ማቋረጥን በሚደግፍ የግዛት ሕግ ዙሪያ ክርክሮችን የሰማ ሲሆን፤ በጽንስ ማቋረጥ ዙሪያ ለብዙ አስርት ዓመታት የዘለቀውን ክርክር ተከትሎ የተቃውሞ ድምጾች ሲስተጋቡ ውለዋል፡፡

    የ2021 የዓለም አቀፍ የፊጎ አዋርድ ተሸላሚ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ማናቸው? - ኖቬምበር 01, 2021

    የ2021 የዓለም አቀፍ የፊጎ አዋርድ ተሸላሚ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ማናቸው? - ኖቬምበር 01, 2021
    ረዳት ፕሮፌሰር ዶክተር መቅደስ ዳባ በቅዱስ ፓውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የማህጸን እና የጽንስ ህክምና ሃኪም እንዲሁም በኢትዮጵያ  የጽንስ እና የማሕጸን ሃኪሞች ማህበር ፕሬዘዳንት ናቸው፡፡ በቅርቡም ዓለም አቀፍ የጽንስ እና የማህጸን ፌደሬሽን በአለም ዙሪያ በዘርፉ በምርመር አስተዋጽኦ አድርገዋል በሚል የጎርጎሮሳዊያኑ 2021 ዓ.ም ከመረጣቸው ባለሞያዎች መሃከል አንዷ በመሆን የፊጎ አዋርድ/ሽልማት ወስደዋል፡፡

    የህፃናትን ስነ-ባህሪና እድገት የሚያጠናው የመጀመሪያው ተቋም - ኦክቶበር 07, 2021

    የህፃናትን ስነ-ባህሪና እድገት የሚያጠናው የመጀመሪያው ተቋም - ኦክቶበር 07, 2021
    ጎጆ የህሙማን መጠለያ ተቋምን በመመስረት በሺዎች ለሚቆጠሩ አቅመ ደካማ ህሙማን ድጋፍ እየሰጠች የምትገኘው ዶክተር ሰላሜነሽ ፅጌ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የህፃናት ስነ-ባህሪና የእድገት ሁኔታን የሚያጠና ተቋም በጥቁር አምበሳ ሆስፒታል ስር እንዲጀመር ያደረገች የህፃናት ሀኪም ናት።

    የአዲስ አበባ መምህራን ስራ ከመጀምራቸው በፊት እንዲከተቡ ስለሚያደርገው መመሪያ ምን ይላሉ? - ኦክቶበር 02, 2021

    የአዲስ አበባ መምህራን ስራ ከመጀምራቸው በፊት እንዲከተቡ ስለሚያደርገው መመሪያ ምን ይላሉ? - ኦክቶበር 02, 2021
    ጥቅምት 1 ትምህርት ከመጀመሩ በፊት የአ.አ ትምህርት ቢሮ መምህራን እና የትምህርት ቤት አስተዳደር አባላት ከስራቸው አንጻር ከፍተኛ የሆነ የኮቪድ 19 ተጋላጭነት እንዳላቸው በመገንዘብ እራሳቸውንም ሆነ ቤተሰባቸውን ከበሽታው እንዲጠብቁ ለማስቻል አስገዳጅ የሆነ የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት እንዲወስዱ አስገዳጅ የሆነ መመሪያ ወጥቷል፡፡ በዚህ ጉዳይ ምምህራኑ ምን ይላሉ?

    ለተቸገሩ ህሙማን እና አስታማሚዎች ማረፊያ የሆነችው ሀኪም - ሴፕቴምበር 03, 2021

    ለተቸገሩ ህሙማን እና አስታማሚዎች ማረፊያ የሆነችው ሀኪም - ሴፕቴምበር 03, 2021
    አሜሪካ በየአመቱ ለአፍሪካ ወጣት መሪዎች በምታዘጋጀው የማንዴላ ፌሎውሺፕ በዚህ አመት ከኢትዮጵያ ከተመረጡት መሀከል ጎጆ የህሙማን መጠለያ ተቋምን የመሰረተችው ዶክተር ሰላሜነሽ ፅጌ አንዷ ናት። ተቋሙ ከኢትዮጵያ የገጠር ከተሞች ለተጨማሪ ህክምና አዲስ አበባ የሚመጡ፣ ማረፊያ በማጣትና ገንዘባቸውን ለህክምና በመጨረስ ለጎዳና ህይወት የሚዳረጉ ህሙማንን በጊዜያዊነት የሚያስጠልል ሲሆን ባለፉት ሶስት አመታት ውስጥ ከ81 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህሙማን ረድቷል።

    'የአማኑኤል ሆስፒታል ታሪኮች' ቆይታ ከአእምሮ ሃኪሙ ዶ/ር ዮናስ ላቀው ጋር - ሴፕቴምበር 01, 2021

    'የአማኑኤል ሆስፒታል ታሪኮች' ቆይታ ከአእምሮ ሃኪሙ ዶ/ር ዮናስ ላቀው ጋር - ሴፕቴምበር 01, 2021
    ብዙ ሰዎች በአማኑኤል የአእምሮ ሆስፒታል ታክመው ከዳኑ በኋላ እዛ መታከማቸውን መናገር ይፈራሉ ይላል ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ድንገት እነዚህ ሰዎች ከሰው ለየት ያለ ነገር ሲናገሩም ሆነ ሲሰሩ ቢታዩ “እሱ/ እሷ ድሮስ ከአማኑኤል አይደል እንዴ የመጡት?” ይባላሉ ይላል ዶ/ር ዮናስ ላቀው፡፡ እንደውም ከነጭራሹም እዛ የምትሰሩት እራሳቹ ‘እብዶች አይደላቹ እንዴ?’ ተብዬም አውቃለሁ ይላል፡፡ ሙሉውን ቃለምልልስ ያድምጡት፡፡

    'ዓለምን በቀጣይ ከሚያሰጓት ወረሽኞች ለመከላከል የሚያጠናው ግሎባል ዋን ሄልዝ' ቆይታ ከፕሮፌሰር ወንድወሰን አበበ ጋር - ኦገስት 26, 2021

    'ዓለምን በቀጣይ ከሚያሰጓት ወረሽኞች ለመከላከል የሚያጠናው ግሎባል ዋን ሄልዝ' ቆይታ ከፕሮፌሰር ወንድወሰን አበበ ጋር - ኦገስት 26, 2021
    ግሎባል ዋን ሄልዝ ኢንሺየቲቭ ወይም አንድ የዓለም ጤና ተነሳሽነት በአሜሪካ ሃገር በሚገኘው በኦሃዮ ዩኒቨርሲቲ አማካኝነት የተመሰረተ ሲሆን ዓላማውም ከአካባቢ፣ ከእንሣት እና ከሰዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው እንደ ኮቪድ 19፣ ኢቦላ፣ የእብድ ውሻ በሽታ፣ በነፍሳት ፣ በውሃ፣ በዓየር..የሚመጡ በሽታዎችን በኢትዮጵያ፣ ኬኒያ፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሜክሲኮ፣ ብራዚል እና ታይላንድ...እየተንቀሳቀሰ የሚያጠና ነው፡፡ ይሄ ተነሳሽነት ከተመሰረተ ዘንድሮ 10ኛ ዓመቱ ይዟል፡፡

    "የፓርኪንሰን ችግር ሰፊ ቢሆንም ስራችንን ከአዲስ አበባ ውጪ እንዳናስፋፋ የበጀት ችግር አለብን" ክብራ ከበደ - ጁላይ 15, 2021

    "የፓርኪንሰን ችግር ሰፊ ቢሆንም ስራችንን ከአዲስ አበባ ውጪ እንዳናስፋፋ የበጀት ችግር አለብን" ክብራ ከበደ - ጁላይ 15, 2021
    የፓርኪንሰን ሕሙማን ድጋፍ ማኅበር በኢትዮጵያ ከተመሰረተ አስራ ሁለት ዓመት ይሆነዋል፡፡ የድርጅቱ መስራች ክብራ ከበደ ትሰኛለች፡፡ ማኅበሩ ከተመሰረተ ጀመሮ በበሽታው ዙሪያ ግንዛቤን ለመፍጠር የእግር ጉዞዎች፣ የውይይት ምሽቶች፣ የምክር አገልግሎቶች የሚሰጥ ሲሆን ለሕሙማኑም የምክር፣ የገንዘብ እና የሕክምና ድጋፍ እንዲያገኙ በማመቻቸት እየሰራ ይገኛል፡፡

    'ከሰኔ 30 በኋላ ምን ይመጣ ይሆን?' ዘላቂ መፍትሄ ያጣው የሃኪሞች ስራ አጥነት - ጁን 26, 2021

    'ከሰኔ 30 በኋላ ምን ይመጣ ይሆን?' ዘላቂ መፍትሄ ያጣው የሃኪሞች ስራ አጥነት - ጁን 26, 2021
    ኢትዮጵያ እጅግ አነስተኛ የሆነ የጤና ባለሞያ ካለባቸው ሃገራት መሃከል ናት፡፡ ይሁንና በሃገሪቱ የህክምና ባለሞያዎች ስራ አጥ ናቸው፡፡ ከወራት በፊት በአማራ ክልል የሕክምና ባለሞያዎች የስራ ዕድል እንዲፈጠርላቸው ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን በዚህ መሰረትም የጤና ሚኒስቴር እና የክልሉ የጤና ቢሮ እስከ ሰኔ 30 ድረስ የሚቆይ የ3 ወራት የስራ እድል አመቻችተው ነበር፡፡ ይሁንና ከቀናት በሁላ የኮንትራት ጊዜያቸው ስለሚያልቅ የስራ አጥነት ስጋት ውስጥ ናገጥሟቸዋል፡፡

    የመጀመሪያው የድንገተኛ እና አደጋ ጽኑ ህክምና መሪ እቅድ ምን ይመስላል? - ጁን 15, 2021

    የመጀመሪያው የድንገተኛ እና አደጋ ጽኑ ህክምና መሪ እቅድ ምን ይመስላል? - ጁን 15, 2021
    በኢትዮጵያ ለመጀምሪያ ጊዜ የድንገተኛ እና ጽኑ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እና ተደራሽነት ለመጨመር የሚያስችል የአምስት ዓመት መሪ ዕቅድ ባለፈው ሳምነት የጤና ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል፡፡  መሪ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግም 200 ሚሊየን ዶላር እንደሚያስፈልግ በኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር የድንገተኛ እና ጽኑ ህክምና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑትን ዶ/ር አለኝታ ገብረየስ ለአሜሪካ ድምጽ ገልጸዋል፡

    "ሱስ ያለኝን ሁሉ ካሳጣኝ በኋላ እራሴን ላጠፋ ሞክሬ ነበር" ከሱስ ሕይወት የወጣ ወጣት - ጁን 11, 2021

    "ሱስ ያለኝን ሁሉ ካሳጣኝ በኋላ እራሴን ላጠፋ ሞክሬ ነበር" ከሱስ ሕይወት የወጣ ወጣት - ጁን 11, 2021
    በትምህርት ላይ ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ፣ ለመዝናናት ወይም ስራ በማጣት ከሚመጣ ጭንቀት እና ድብርት ለመውጣት በሚል እና በተለያዩ ሌሎች ምክንያቶች ወጣቶች ወደ ሱስ ዓለም ይገባሉ፡፡ ይሁንና ከጊዜ በኋላ ከገቡበት መውጣት እየፈለጉም ሲያቅታቸው እና ሲፈተኑ ይታያል፡፡ ኤደን ገረመው ሁለት ከዚህ ቀደም በሱስ ሕይወት ውስጥ የነበሩና በሱስ የተነሳ ሕይወታቸውን እስከማጥፋት ከደረሱ በኋላ የወጡ ወጣቶችን አነጋግራ ተከታዩን አሰናድታለች፡፡

    'ወጣቶችን ከሱስ ህይወት ለመታደግ በነጻ አገልግሎት የሚሰጠው ተቋም ድጋፍን ይሻል' ሲስተር ይርገዱ ሃብቴ - ጁን 05, 2021

    'ወጣቶችን ከሱስ ህይወት ለመታደግ በነጻ አገልግሎት የሚሰጠው ተቋም ድጋፍን ይሻል' ሲስተር ይርገዱ ሃብቴ - ጁን 05, 2021
    የመጨረሻ ልጃቸው አስከፊ የሆነ የሱስ ሕይወት ገብቶ ከ10 ዓመት በላይ ከባድ ጊዜ አሳልፈዋል፡፡' ልጄ ጠፋ' ብዬ አምላኬን ብዙ ጊዜ አማርሬዋለሁ ይላሉ፡፡ ያ ቀን አልፎ ታዲያ ልጃቸው ከነበረበት ወጥቶ አሁን ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሶላቸዋል፡፡ ይሄ የሕይወት ተሞክሯቸው ግን በሱስ የተጎዱ ወጣቶችን እየሰበቡ በማሳረፍ የጤና እና የስነ ልቦና ድጋፍ የሚያገኙበትን አዲስ ሕይወት የእጽ እና የአልክሆል እና የሱሰኝነት ህክምና ማገገሚያ ማዕከልን ወደ መመስረት መርቷቸዋል፡፡

    የኩላሊት ህክምና አገልግሎት ከአዲስ አበባ ውጪ ላሉ ከተሞችን ለማዳረስ ያሰበው ኢትዮጵያን ኪድኒኬር - ጁን 04, 2021

    የኩላሊት ህክምና አገልግሎት ከአዲስ አበባ ውጪ ላሉ ከተሞችን ለማዳረስ ያሰበው ኢትዮጵያን ኪድኒኬር - ጁን 04, 2021
    ኢትዮጵያን ኪድኒ ኬር ከተመሰረተ ስምንት ወራት ሆነው፡፡ ተቋሙ በኩላሊት ህክምና ላይ ግንዛቤን ለመፍጠር፣ እንዲሁም ጥናቶችን ለመስራት እና ከአዲስ አበባ ውጪ ላሉ ህሙማን የእጥበት አገልግሎት እና የህክምና ተደራሽነትን ለመፍጠር እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ የተቋሙ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር እሴተ ጌታቸው ይናገራሉ፡፡

    ያልተዘመረላቸው ጀግና ተሸላሚ ዶ/ር ትልቅሰው ተሾመ ማናቸው? - ጁን 03, 2021

    ያልተዘመረላቸው ጀግና ተሸላሚ ዶ/ር ትልቅሰው ተሾመ ማናቸው? - ጁን 03, 2021
    ዶ/ር ትልቅሰው ተሾመ በኢትዮጵያ በስኳር ህመም እና በሌሎች የጤና ችግሮች ምክንያት የሚከሰት የዓይነስውርነት ችግረን ለመቅረፍ ከ14 ዓመት በፊት የመጀመሪያውን የሬቲና ህክምና ያስጀምሩ ሃኪም ናቸው፡፡ እስከዛሬ ድረስም ከ7000 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የቀዶ ጥገና አገልግሎትን በመስጠት ህሙማንን ወደ ውጪ ሃገር ከሚደረጉ ጉዞዎችና ከዓይነስውርነት እየታደጉ ይገኛሉ፡፡ የአሜሪካ የዓይን ህክምና አካዳሚ በጎርጎሮሳዊያኑ 2020 ዓ.ም ያልተዘመረላቸው ጀግና ሲል ሸልሟቸዋል፡፡

    በአሜሪካ የቤት ለቤት ማዋለድ አገልግሎት የምትሰጠው ትግስት ቶሌራ - ሜይ 06, 2021

    በአሜሪካ የቤት ለቤት ማዋለድ አገልግሎት የምትሰጠው ትግስት ቶሌራ - ሜይ 06, 2021
    ትግስት ቶሌራ በአሜርካ ሃገር በአሪዞና ግዛት ተክሰን ከተማ ነዋሪነቷን ያደረገች አዋላጅ ሃኪም ናት፡፡ በምትኖርበት በተክሰን ከተማም ኦዳ በረዝ የተሰኘ የቤት ለቤት የማዋለድ አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም የከፈተች ሲሆን እስካሁን ድረስም ወደ 60 የሚጠጉ ሕጻናትን አዋልዳለች፡፡